አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የታክስ ኦዲት ወሳኔ ጥራትን ለማሳደግ የሚያስችል ስልጠና እየተሰጠ ነው

ቢሮው በታክስ ኦዲት አፈፃፀም የሚስተዋሉ ክፍተቶችንና የኦዲት ውሳኔ ጥራትን ማሳደግ ይቻል ዘንድ ከኤች.ኤስ. ቲ አማካሪ የግል ኩባንያ ጋር በመተባበር ከዋና ቢሮና ከሁሉም ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ለተወጣጡ የኦዲት ባለሙያዎች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል ።
ስልጠናው በኩባንያው ሲኒየር የታክስ ማናጀር በአቶ ማሞ አብዲ እየተሰጠ ሲሆን ዓላማውም የታክስና ኢንተሊጀንስ ኦዲተሮቹ በታክስ ኦዲት አፈፃፀምና ውጤታማነት ፣ በአለም አቀፍ የፋይናንስ ሪፖርት አሰራር እንዲሁም በደንበኞች አገልግሎት ዙሪያ በቂ ክህሎትና ዕውቀትእንዲኖራቸው ለማስቻል ነው ብለዋል ።
አያይዘውም ከስልጠናው መልስ ባለሙያዎቹ የህግተገዥነትን በማሳደግ በፈቃደኝነት ግብሩን የሚከፍል ማህበረሰብ መፍጠር ፣ ጥራት ያለው የኦዲት ውሳኔና ሪፖርት ማውጣት ፣ ፍትሀዊ የሆነ የታክስ ስርዓት እንዲሰፍን ማስቻል ፣ ሙያው የሚጠይቀውን ስነ ምግባር በመላበስ የተጣለባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት እንዲሁም ሙያዊ ብቃታቸውን በማሳደግ በገቢ ዘርፍ የሚታዩ የአልግሎትና የመልካም አስተዳደር ክፍተቶችን በመለየትና በመሙላት የሚጠበቀውን ገቢ በአግባቡ ለመሰብሰብ ማስቻል እንደሆነ አስገንዝበዋል ።
ስልጠናው ለ3ቀናት የሚሰጥ ሲሆን ከዋና ቢሮና ከሁሉም ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ለተወጣጡ የታክስ ኦዲትና ኢንቨስትጌሽን ኦዲት ባለሙያዎች እየቸሰጠ ይገኛል ።

Related Articles

አዲስ አበባ: ሳርቤት,  የኦሮሚያ ቢሮዎች ጊቢ ዉስጥ

ስልክ ቁጥር : 011-369-15-18/ 011 369- 18-15

ፋክስ ቁጥር: +251-11-371-78-80

ፖ..ቁ: 27475

Email: Oromiarevenues@gmail.com

ፊንፊኔ, ኦሮሚያ

Oromia Revenue Bureau by ORB ICT