
ስልጠናው በኩባንያው ሲኒየር የታክስ ማናጀር በአቶ ማሞ አብዲ እየተሰጠ ሲሆን ዓላማውም የታክስና ኢንተሊጀንስ ኦዲተሮቹ በታክስ ኦዲት አፈፃፀምና ውጤታማነት ፣ በአለም አቀፍ የፋይናንስ ሪፖርት አሰራር እንዲሁም በደንበኞች አገልግሎት ዙሪያ በቂ ክህሎትና ዕውቀትእንዲኖራቸው ለማስቻል ነው ብለዋል ።
አያይዘውም ከስልጠናው መልስ ባለሙያዎቹ የህግተገዥነትን በማሳደግ በፈቃደኝነት ግብሩን የሚከፍል ማህበረሰብ መፍጠር ፣ ጥራት ያለው የኦዲት ውሳኔና ሪፖርት ማውጣት ፣ ፍትሀዊ የሆነ የታክስ ስርዓት እንዲሰፍን ማስቻል ፣ ሙያው የሚጠይቀውን ስነ ምግባር በመላበስ የተጣለባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት እንዲሁም ሙያዊ ብቃታቸውን በማሳደግ በገቢ ዘርፍ የሚታዩ የአልግሎትና የመልካም አስተዳደር ክፍተቶችን በመለየትና በመሙላት የሚጠበቀውን ገቢ በአግባቡ ለመሰብሰብ ማስቻል እንደሆነ አስገንዝበዋል ።
ስልጠናው ለ3ቀናት የሚሰጥ ሲሆን ከዋና ቢሮና ከሁሉም ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ለተወጣጡ የታክስ ኦዲትና ኢንቨስትጌሽን ኦዲት ባለሙያዎች እየቸሰጠ ይገኛል ።